Semada Woreda Finance and Economic Development Office

በኩር
(Jan 06, 2025)

ግልጽ ጨረታ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎ ማስታወቂያ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎

በደቡብ ጎንደር አስተዳደር ዞን የስማዳ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ግ/ን/አስተዳደር ቡድን በ2017 በጀት ዓመት ለስማዳ ወረዳ ሴክተር መ/ቤቶች አገልግሎት የሚዉሉ በመደበኛ በጀት በካልም በጀት፣ በሪድ ፕላስ በጀት

  • ሎት 1. የጽህፈት መሳሪያ፣
  • ሎት 2. የግንባታ እቃዎች፣
  • ሎት 3. ኤሌክትሮኒክስ፣
  • ሎት 4. የውሃ እቃ፣
  • ሎት 5 የጽዳት ዕቃ፣
  • ሎት 6 የመኪና እና የሞተር ጎማ፣
  • ሎት 7 የተዘጋጀ ፈርኒቸር፣
  • ሎት 8 የስፖርት ዕቃ፣
  • ሎት 9 ብሎኬት፣
  • ሎት 10 የተዘጋጁ ልብሶች፣
  • ሎት 11 የሙጌ አሸዋ፣
  • ሎት 12 የተከሰከሰ ጠጠር እና 
  • ሎት 13 ጥቁር ድንጋይ በግልጽ ጨረታ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡ 

በመሆኑም ተጫራቾች ማሟላት የሚፈለግባቸው መስፈርቶች፡-

1. ህጋዊ ወቅታዊ የታደሰ በዘርፉ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡

2. የዘመኑን ግብር የከፈሉና ቲን ካርድ ማቅረብ የሚችሉ፡፡

3. ተጫራቾች የሞሉት ዋጋ 200,000.00 /ሁለት መቶ ሽህ ብር/ እና በላይ ከሆነ የቫት ተመዝጋቢ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡

4. ተጫራቾች የጨረታ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎ ሠነዳቸውንና ሌሎች መረጃዎቻቸውን በፖስታ በማሸግ ይህ የጨረታ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎ ማስታወቂያ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 ተከታታይ ቀናት በስማዳ ወረዳ ግ/ን/አስ/ደ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 26 ለሥራው በተዘጋጀው ሣጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው፡፡

5. ጨረታ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎ው በ16ኛው ቀን ከጠዋቱ 3፡00 ታሽጎ 3፡30 ይከፈታል፡፡

6. ተጫራቾች ከሚያቀርቡት የመወዳደሪያ ሀሃብ ስማቸውን ፣ፊርማቸውን ማህተማቸዉንና ሙሉ አድራሻቸውን ማስፈር አለባቸው፡፡

7. የጨረታ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎ው ጊዜ ከተጠናቀቀ በኋላ ተጫራቾች ባቀረቡት የመወዳደሪያ ሀሣብ ላይ ለውጥ ማሻሻያ ማድረግና ከጨረታ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎ው እራሣቸውን ማግለል አይችሉም ሥርዝ ድል ፍፁም 
የተከለከለ ነዉ፡፡

8. ጨረታ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎ውን ለማዛባት የሚሞክሩ ተጫራቾች ከጨረታ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎ ውጭ እንደሚሆኑና ለወደፊቱም በመንግስት የግዥ ጨረታ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎ እንዳይሳተፉ የሚደረጉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡

9. ተጫራቾች ለሥራው የተዘጋጀውን ሠነድ የማይመለስ 50.00 /አምሳ ብር/ ብቻ በመክፈል ዘወትር በሥራ ሰዓት‍‌‌‌‍‍‍‍‌‍‌‌‍‌‍‍‌ ስ/ወ/ገ/ያዥ ቢሮ ቁጥር 12 መግዛት ይችላሉ፡፡

10. ተጫራቾች ከሚያቀርቡት አጠቃላይ ዋጋ አንድ በመቶ የጨረታ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎ ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ወይም በጥሬ ገንዘብ ለዋና ገንዘብ ያዥ ማስያዝና ያስያዙበትን ኮፒ ፖስታ ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡

11. ተጫራቾች ጨረታ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎ውን ካሸነፉ በኋላ አስር በመቶ የውል ማስከበሪያ በጥሬ ገንዘብ በባንክ በተረጋገጠ /ሲፒኦ/ ማቅረብና ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡

12. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎ውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

13. ጨረታ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎ው ተጫራቾች ህጋዊ ወኪሎቻቸው ቢገኙም ባይገኙም ይከፈታል፡፡

14. ጨረታ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎ው የሚከፈትበት ቀን የበዓል ቀን ከሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን ይሆናል፡፡

ለበለጠ ማብራሪያ በሥልክ ቁጥር 058 667 01 67 ደውሎ ወይም ግ/ን/አስ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 26 በአካል ጠይቆ መረዳት ይቻላል፡፡

የስማዳ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት