
Amanuel Mental Specialized Hospital
አዲስ ዘመን
(Aug 10, 2024)
የግልፅ ጨረታ ማስታወቂያ
የአማኑኤል የአእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ለ2017 በጀት ዓመት የጋራዥ አገልግሎት ግዥ በጨረታ ቁጥር AMSH/ 001/2017 በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
ስለዚህ፡–
- በዘመኑ የታደሰ የንግድ ፈቃድ እና በዘርፉ የተመዘገባችሁበትን የሚገልጽ ፍቃድ፡፡
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር Tin/ያላቸው፡፡
- የዘመኑን ግብር የከፈሉ ለመሆናቸው ማስረጃ፡፡
- የመድን ሽፋን ያለው መሆን አለበት ፡፡
- የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ብር 20,000 /ሀያ ሺህ ብር/ በሲ.ፒ.ኦ ፤ በጥሬ ገንዘብ ወይም የባንክ ዋስትና ማቅረብ አለበት።
- የጨረታው ማስከበሪያ ዋስትና 90 ቀናት⁄ ዘጠና| ቀናት ፀንቶ የሚቆይ መሆን አለበት፡፡
- የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 100 /መቶ ብር/ በመክፈል መውሰድ ይችላሉ።
- ተጫራቾች የአገልግሎት ዋጋችሁን ሆስፒታሉ ለዚህ ጨረታ ባዘጋጀው ሰነድ የድርጅታችሁን ማህተምና ፊርማ በማድረግ መሙላት ይኖርባችኋል።
- ማንኛውም ተጫራች ሀሣቡን በአንድ ፖስታ ውስጥ ወይም ብቻ ለብቻ ሁለት ቅጂዎች ቴክኒክ ዋናና ኮፒ እና ፋይናንሻል ሰናዳችሁን ዋናና ኮፒ በማለት እያንዳንዱ ገፅ ላይ የድርጅቱን ማህተምና ፊርማ በማድረግ በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ በአማኑኤል አእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በግዥ ዳ/ዳ ቢሮ በተዘጋጀው በጨረታው ሣጥን ውስጥ ዘወትር በስራ ሰዓት ማስገባት ትችላላችሁ::
- ጨረታው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ የስራ ቀናት ሆኖ በ15ኛው ቀን ላይ ከቀኑ 10፡30 ሰዓት የጨረታ ሣጥን ተዘግቶ በ16ኛው ቀን በ4፡00 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በግዥ ዳዳ ቢሮ ጨረታው የሚከፈት ይሆናል፡፡ ጨረታው የሚዘጋበትና የሚከፈትበት ቀን የበዓላት ቀን ከሆነ የሚቀጥለው የስራ ቀናት የሚከፈትና የሚዘጋ ይሆናል፡፡
- ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ በግዥ ዳ/ዳይሬክተር ቁጥር 7 ድረስ በአካል በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 011 868 5387/011 278 8056 በመደወል ማግኘት ይችላሉ፡፡
መስሪያ ቤቱ የተሻለ አማራች ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብት አለው፡፡
የአማኑኤል የአእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል