Central Ethiopia Regional Government Gurage Zone Finance Department

አዲስ ዘመን
(Jan 07, 2025)

የጨረታ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎ ማስታወቂያ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎

የጨረታ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎ ቁጥር፡-5-2017

የጉራጌ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለጉራጌ ዞን ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ እያስተዳደረው ያለው የወልቂጤ እስታዲየም ውስን ስራዎች ጥገና ለማከናወን ተቋራጮችን አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡

ስለዚህ በጨረታ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎ው መወዳደር የምትፈልጉ ተጫራቾች በማመልከቻ ሲጠይቁ ማሟላት የሚገባቸው መስፈርቶች፡

1. ህጋዊ ምዝገባ ማረጋገጫ ማቅረብ የሚችሉ፤

2. በደረጃቸው ጂሲ-5 እና ከዚያ በላይ ደቃድ ያላቸው፤

3 የዘመኑን ንግድ ፈቃድ ያደሱ ሆነው ዋናውንና ኮፒውን ማቅረብ የሚችሉ፤

4. የዘመኑ የኮንስትራክሽን ሚኒስቴር እና የቫት ተመዝጋቢ መሆናቸውን የሚገልጽ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፤

5. በጨረታ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎ መወዳደር የሚፈልጉ ተወዳዳሪዎች የሚገዙት የጨረታ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎ ሰነድ ጠቅሰው በማመልከቻ ሲጠይቁ ተወካዮች ከሆኑ ከድርጅቱ ህጋዊ ውክልና ይዘው መቅረብ አለባቸው።

6. ተጫራቾች የጨረታ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎ ሰነዱን የማይመለስ ብር 500.00 /አምስት መቶ ብር/ በጉራጌ ዞን ገቢዎች በመክፈል ጉራጌ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ቢሮ ቁጥር 18 ቀርበው መግዛት ይችላሉ፡፡

7. ተጫራቾች በሚያቀርቡት ሰነድ ላይ ስማቸውን፣ ፊርማቸውን እና አድራሻቸውን ማስፈርና የድርጅቱን ማህተም ማስቀመጥ አለባቸው፡፡

8. በጨረታ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎ ሰነዱ ላይ ምንም አይነት ስርዝ ድልዝ መኖር የለበትም፡፡

9. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎ ሰነዱን እና ሌሎች ተፈላጊ መረጃዎችን ማለትም 1 ፋይናንሻል ኦሪጅናል እና 2 ኮፒ በጥንቃቄ በተናጠል በታሸገ ፖስታ 1 ቴክኒካል ኦርጅናል እና 2 ኮፒ በጥንቃቄ በተናጠል በታሸገ ፖስታ በመለያየት በጥንቃቄ በታሸገ እናት ፖስታ ከጉራጌ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ቢሮ ቁጥር 18 በተዘጋጀው የጨረታ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎ ሳጥን ውስጥ ዘወትር በስራ ሰዓት‍‌‌‌‍‍‍‍‌‍‌‌‍‌‍‍‌ ይህ የአካባቢ ማስታወቂያ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 21 ቀናት ውስጥ ማስገባት ይጠበቅበታል፡፡

10. ከተራ ቁጥር 1-8 የተጠቀሱትን መስፈርቶች ሙሉ በሙሉ ያላሟሉ ተጫራቾች ከውድድር ውጪ ይሆናሉ፡፡

11. የጨረታ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎ ማስከበሪያ ብር 150,000.00 /አንድ መቶ ሃምሳ ሺህ ብር/ በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ወይም የግዥ መምሪያ በሚፈቅደው ዋስትና 120 ቀናት ጸንቶ የሚቆይ በጉራጌ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ስም ተዘጋጅቶ ከሚያቀርቡት ኦሪጅናል ቴክኒካል ፕሮፖዛል ጋር በተናጠል ታሽጎ መቅረብ ይኖርበታል፡፡

12. ጨረታ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎ው 21ኛው ቀን 800 ሰዓት ታሽጎ በዚያኑ ቀን ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት 830 ሰዓት ላይ በጉራጌ ዞን ፋይናንስ መምሪያ አዳራሽ ውስጥ በይፋ ይከፈታል፡፡ ተቋራጮች (ወኪሎቻቸው) ባይገኙም ጨረታ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎ው ይከፈታል፡፡

13. ጨረታ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎ው የሚከፈትበት ቀን ቅዳሜና እሁድ /የህዝብ በዓል/ ላይ ከዋለ ጨረታ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎ው የሚከፈተው በሚቀጥለው የሥራ ቀን ከላይ በተጠቀሰው ሰዓት ይሆናል፡፡

ማሳሰቢያ

የጉራጌ ዞን ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ ከሚከታተላቸው ፕሮጀክቶች ውስጥ በአፈጻጸማው ምክንያት 3 ዙር ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷቸው ውል ያቋረጡ ተጫራቾች መወዳደር አይችሉም፡፡

  • /ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎ውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው።
  • በጨረታ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎ው ሂደት ውስጥ ተሻሽሎ የወጣው የክልሉ መመሪያ ተግባራዊ የሚደረግ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
  • ለበለጠ መረጃ /ቤቱ ድረስ በአካል በመቅረብ ወይም በስልክ ቁጥር 0113–30-01-12 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ።

በማዕ/ኢት///የጉራጌ ዞን ፋይናንስ መምሪያ