Wolaita Zone Sodo Surrounding Woreda FEDB

አዲስ ዘመን
(Jan 23, 2025)

ለበርካታ ዓመታት (ዕድሜ ጠገብ ) እንጨቶች
ሽያጭ የወጣ ግልጽ ጨረታ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎ ማስታወቂያ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎

ወላይታ ዞን የሶዶ ዙሪያ ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት በኮካቴ ማራጫሬ ችግኝ ጣቢያ ውስጥ ለበረካታ ዓመታት (ዕድሜ ገብ) እንጨቶች ማለትም ፓይነስ ፓቹላ፤ ባህርዛፍ የፈረንጅ ጽድ እና ግራቭሊያ እንጨቶችን ለተለያዩ ዓለማ ላይ የሚውል ደን ዛፎችን በግልጽ ጨረታ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡

ስለሆነም በጨረታ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎ው መሳተፍ የሚፈልግ ማንኛውም ተጫራች፡-

  1. ማንነቱን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ ፎቶ ኮፒ እና የጨረታ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎ ሰነድ የገዙበት ደረሰኝ ኮፒ ማቅረብ አለባቸው፡፡
  2. ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ ለ15 ተከታታይ የሥራ ቀናት ከላይ የተገለጹ ፓይነስ ፓቹላ ፤ባህርዛፍ የፈረንጅ ጽድ እና ግራቭሊያ በዝርዝር የያዘውን የመወዳደሪያ ሰነድ ሶዶ ዙሪያ ወረዳ ገቢዎች ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 2 በመቅረብ የማይመለስ ብር 100 (አንድ መቶ) በመክፈል መውሰድ ይችላሉ፡፡
  3. ተጫራቾች የጨረታ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎ ማስከበሪያ ለጨረታ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎ ከሚያስገበው ገንዘብ መጠን ጠቅላላ 4% (አራት በመቶ) በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ወይም በጥሬ ገንዘብ በጽ/ቤቱ ደረሰኝ ገቢ በማድረግ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
  4. የጨረታ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎ ሣጥን ጋዜጣው ከወጣበት 15 ተከታታይ ሥራ ቀናት ቀጥሎ በሚውለው የሥራ ቀን ከሰዓት‍‌‌‌‍‍‍‍‌‍‌‌‍‌‍‍‌ 8፡30 ሰዓት ታሽጐ በዕለቱ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ሶዶ ዙሪያ ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት ከሰዓት 8፡45 ሰዓትበቢሮ ቁጥር 4 ይከፈታል፡፡
  5. የጨረታ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎ው አሸናፊ ማሸነፉ እንደተረጋገጠ ያሸነፈበትን ዋጋ በሶዶ ዙሪያ ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት የባንክ አካውንት ሙሉ በሙሉ ገቢ ሲያደርግ ያሸነፈውን ደን እንጨቶችን ወዲያውኑ ይረከባል፡፡ ሌሎች ዝርዝር ሂደቶች በጨረታ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎ ሰነድ የሚካተቱ ይሆናል፡፡
  6. አሸናፊ በሆኑበት ደን እንጨቶች ሽያጭ በተሰጠው ጊዜ ገደብ ውስጥ ስምምነት ውል ለመግባት ፍቃደኛ ካልሆኑ የጨረታ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎ ማስከበሪያ ለመንግሥት ገቢ ይሆናል፡፡
  7. ተጫራቾች የጨረታ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎ ሰነዱን ገዝተው የገዙበትን ደረሰኝ በመያዝ ሶዶ ዙ/ወ/አከባቢ ጥበቃ ጽ/ቤት ጋር በመሆን በኮካቴ ማራጫሬ ችግኝ ጣቢያ ውስጥ ያለውን የፓይነስ ፓቹላ ፤ባህርዛፍ የፈረንጅ ጽድ እና ግራቭሊያ እንጨቶችን ሄደው ማየት ይችላሉ፡፡
  8. ጽ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎ውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር 046-180-6026 ደውለው
ማነጋገር ይችላሉ፡፡
ወላይታ ዞን ሶዶ ዙሪያ ወረዳ ፋይ/ጽ/ቤት