• Amhara

Yigem Health Care Center

አዲስ ዘመን
(Jan 06, 2025)

ግልጽ የጨረታ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎ ማስታወቂያ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎

በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በሰ/ሸዋ ዞን የመንዝ ማማ ምድር ወረዳ የይገም ጤና አጠባበቅ ጣቢያ ለአገልግሎት የሚውሉ፡-

  • ሎት 1 የፅህፈት መሳሪያዎች፣
  • ሎት 2 የደንብ ልብስ፣
  • ሎት 3 የተለያዩ ህትመቶች፣
  •  ሎት 4 የፅዳት እቃዎች በግልፅ ጨረታ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎ አወዳድሮ ለመግዛትና ለማሳተም ይፈልጋል፡፡

በዚህ መሰረት፡-

  1. በዘርፉ የተሰማሩና የዘመኑን ግብር የከፈሉበትን ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  2. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /ቲን ነምበር ያላቸው፡፡
  3. የግዥው መጠን ከብር 200,000 /ሁለት መቶ ሺህ ብር/ እና በላይ ከሆነ የቫት ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  4. ተጫራቾች በጨረታ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎ ለመሳተፍ ከላይ ከተራ ቁጥር 1 እስከ 3 የተጠቀሱትና ሌሎች የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
  5. የሚገዙ እቃዎችን እና የሚታተሙት ዓይነትና ዝርዝር መግለጫ ከጨረታ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎ው ሰነዱ ላይ ማግኘት ይችላሉ፡፡
  6. ተጫራቾች የጨረታ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎ ማስከበሪያ ዋስትና የእቃውን ጠቅላላ ዋጋ 1% በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትእዛዝ / CPO/ ወይም በጥሬ ገንዘብ ለእያንዳንዱ ሎት ማስያዝ አለባቸው፡፡
  7. ተጫራቾች በሚያቀርቡት ሰነድ ላይ ስማቸውን፣ ፊርማቸውንና የድርጅታቸውን ማህተም ማድረግ አለባቸው፡፡
  8. በመጫረቻ ሰነዱ ላይ ምንም አይነት ስርዝ ድልዝ መኖር የለበትም፡፡
  9. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎ ሰነዱን ለእያንዳንዱ ሎት አንድ ወጥ በሆኑ ሁለት ፖስታዎች ማለትም አንድ ኦሪጅናል እና አንድ ኮፒ በማለት በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ በይገም ጤና አጠባበቅ ጣቢያ ቢሮ ቁጥር 1 በተዘጋጀው የጨረታ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎ ሳጥን ዘወትር በስራ ሰዓት‍‌‌‌‍‍‍‍‌‍‌‌‍‌‍‍‌ ይህ ማስታወቂያ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎ አየር ላይ ከዋለበት ቀን ጀምሮ ለ16 ተከታታይ ቀናት እስከ 4፡00 ሰዓት ድረስ የጨረታ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎ውን ሰነድ ገቢ ማድረግ ይችላሉ፡፡
  10. ጨረታ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎ው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በ16ኛው ቀን ጨረታ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎ው በተዘጋበት ቀን በ4፡30 ሰዓት ላይ በመንዝ ማማ ምድር ወረዳ በይገም ጤና አጠባበቅ ጣቢያ ቢሮ ቁጥር 1 ውስጥ በይፋ ይከፈታል፡፡ ባይገኙም ከመከፈት አይታገድም፡፡
  11. ጨረታ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎ው የሚከፈትበት ቀን ቅዳሜና እሁድ ወይም የህዝብ በዓል ላይ ከዋለ ጨረታ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎ው የሚከፈተው በሚቀጥለው የስራ ቀን ከላይ በተጠቀሰው ሰዓት ይሆናል፡፡
  12. ተጫራቾች የጨረታ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎ ሰነዱን በማይመለስ ብር 50 /ሃምሳ ብር ብቻ/ በመክፈል ከመንዝ ማማ ምድር ወረዳ በይገም ጤና አጠባበቅ ጣቢያ ቢሮ ቁጥር 1 መግዛት ይችላሉ፡፡
  13. ተጫራቾች ያሸነፉትን ንብረት በራሳቸው ወጪ ወደ ጤና ተቋሙ በማምጣት ማስረከብ አለባቸው፡፡
  14. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታ‏‎‎‎‏‏‏‏‎‏‎‎‏‎‏‏‎ውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው፡፡

ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር፡-09-11-09-41-51/ 0920-33-20-76 ደውስው ይጠይቁ፡፡
በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በሰ/ሸዋ ዞን የመንዝ ማማ ምድር ወረዳ የይገም ጤና አጠባበቅ ጣቢያ