Addis Zemen (Apr 14, 2025)

ሀገራዊ ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ  

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት በጋሞ ዞን ቁጫ አልፋ ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት በ2017 በጀት ዓመት መደበኛ ካፒታል በጀት እና ካፒታል ፕሮጀክቶች ማለትም ለአስር ህንጻ ግንባታ እና ለት/መንገድ ልማት ጽ/ቤት መንገድ ስራ እና በልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም የተለያዩ ማቴሪያሎዎችን በሀገራዊ ግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት እና ለማሰራት ይፈልጋል።

  1. ለወረዳው አስ/ር ጽ/ቤት ግንባታ የሚውል፡- አሸዋ፣ ጠጠር፣ የፍልጥ ድንጋይ እና ብሎኬት ግዥ፣
  2. የህንጻ መሣሪያዎች እና የቧንቧ ዕቃዎች
  3. ዘመናዊ የንብ ቀፎ
  4. የደን ችግኝ ዘር እና የምግብ ምርጥ ዘር
  5. የመንገድ ከፈታ አፈር ሥራ የዶዘር ማሽነሪ ኪራይ/መኮናተር

ስለሆነም በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልግ ሁሉ ተሻሽሎ በወጣው በመንግሥት ግዥ አፈጻጸም መመሪያ ቁጥር 28/2010 ዓ/ም መሰረት፡-

  1. የታደሰ ንግድ ፈቃድ ያላቸው
  2. የዘመኑን ግብር የከፈሉበትን መረጃ ማቅረብ የሚችሉ፤
  3. የግብር ከፋይነት ምዝገባ ቁጥር /Tin Number/ያላቸው፤
  4. የቫት ተመዝጋቢ የሆኑበትን መረጃ አያይዞ ማቅረብ የሚችሉ፤
  5. ከሽያጭ ዋጋ ላይ ለመንግሥት ግብር 2% ለመክፈል ፈቃደኛ የሆኑ፤
  6. የንግድ ምዝገባ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፤
  7. የዕቃ አቅራቢነት ምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፤
  8. የጨረታ ሁኔታ በአይተም ወይም በጥቅል ሊሆን ይችላል፤
  9. የብቃት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፤
  10. ለዶዘር ማሸን ከመንግሥት መ/ቤት የመልካም የስራ አፈጻጸም ማቅረብ የሚችሉ፤ ተጫራቹ የግል ሊብሬ ማቅረብ የሚችል መሆን አለበት፤
  11. የጨረታውን ሰነድ ዋና እና ኮፒ በመለየት ኦርጂናሉን በአንድ እናት ፖስታ ውስጥ በማስገባት በሰም በታሸገው ኤንቨሎፕ ፖስታ ውስጥ በማድረግ በቁጫ አልፋ ወረዳ/ፋ/ጽ/ቤት ቢሮ-5 ላይ ለዚህ ተብሎ በተዘጋጀው የጨረታ ሣጥን ውስጥ ማስገባት ይችላሉ።
  12. በጨረታ ሂደቱ ላይ አሸናፊ የሆነው ድርጅት ከጠቅላላ ዋጋ ላይ የውል ማስከበሪያ 10% የማስያዝ ግዴታ አለበት፤
  13. ጨረታው በአየር ላይ የሚቆየው ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 /አስራ አምስት/ ተከታታይ የሥራ ቀናት ይሆናል።
  14. ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነድ የማይመለስ 200/ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 /አስራ አምስት/ ተከታታይ የሥራ ቀናት ውስጥ ወደ ቀጫ አልፋ ወረዳ ፋ/ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር-5 ድረስ በመቅረብ የተዘጋጀውን ሰነድ መግዛት የሚችሉ ይሆናሉ።
  15. ተጫራቾች ለእያንዳንዱ የጨረታ ሰነድ የጨረታ ማስከበሪያ የሚመለስ በጥሬ ወይም የኢትዮ ባንከ ቼክ 20,000.00 /ሃያ ሺህ ብር/ ብቻ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የተረጋገጠ ህጋዊ CPO ለሚሳተፉበት ከጨረታ ሰነድ ጋር አያይዞ የማቅረብ ግዴታ አለባቸው።
  16.  የጨረታ ሣጥኑ የሚታሸገው የጨረታ ማብቂያ በ15ኛው ቀን ከቀኑ 10:00 ሰዓት ይሆናል።
  17. ጨረታው የሚከፈተው በ16ኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይሆናል።
  18. የጨረታው አሸናፊ ድርጅት ወይም ግለሰብ ዕቃውን እስከ ቁጫ አልፋ ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት ድረስ የጫኚ አውራጅና የጭነት ወጪን በመሸፈን ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
  19. ተጫራቾች ወይም የጨረታ ወኪል ያለመገኘት ጨረታውን መከፈት አያስተጓጉልም።
  20. 16ኛው ቀን ሰንበት ወይም በዓል ከሆነ በቀጣይ የሥራ ቀን የሚከፈት ይሆናል።

ማሳሰቢያ፡-

  • የደን ችግኝ ዘር እና የምግብ ምርጥ ዘር ግዥ ጨረታ ተወዳዳሪዎች ከቫት ነጻ የሆኑበትን የድጋፍ ደብዳቤ መረጃ አያይዞ የማቅረብ ግዴታ አለባቸው።
  • ለዶዘር ማሽነሪ ኪራይ ሞዴል ከ2010 ወዲህ ስሪት CAT D8R በአሁኑ ገበያ ያለ መሆን አለበት። ለዶዘር ማሽን የጭነት ዋጋ በአከራዩ የሚሸፈን ይሆናል።
  • የዶዘር ማሽን አሸናፊ ተጫራች በውድድሩ ካሸነፉ በሰባት ቀናት ውስጥ ለአሰሪው መ/ቤት ማሽኑን የማቅረብ ግዴታ አለባቸው።
  • የጨረታው አሸናፊ ድርጅት ወይም ግለሰብ ዕቃው ከጥራትና ደረጃ ዝቅ ቢል፣ ዕቃው ቢጎድል ከተዋወለው ከውሉ ጊዜው ቢያልፍ በሕግ መሰረት ለመንግስት ከገባው ከጠቅላላ ውል ገንዘብ ላይ 20% የሚደርሰውን ብር ተቀጥቶ ገንዘብ ተመላሽ ለማድረግ በፍ/ህ/ቁጥር 2005 መሰረት የፀና ይሆናል።
  • ጽ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው።
  • ለበለ መረጃ ስልክ፡- 09 16 66 99 82/ 09 26 36 60 87/ 09 76 13 56 48/ 09 84 66 61 89 ደውለው ይጠይቁ

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጋሞ ዞን የቁጫ ወ/ፋ/ጽ/ቤት