Addis Zemen (Mar 21, 2025)

ለመጀመሪያ ጊዜ የወጣ ሀገር አቀፍ ግልፅ

ጨረታ ማስታወቂያ መለያ ቁጥር GGWW/0027/2017

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጉራጌ ዞን የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት በ2017 በጀት ዓመት በመደበኛ በጀት ለሚያሰራው ከአረዳ እስከ ጅማ ድረስ ያለው የመንገድ ግንባታ ስራ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል።

ስለሆነም ተጫራቾች፡-

  1. የዘመኑን ንግድ ፍቃድ ያሳደሱ የቫት እና ቲን ነምበር ተመዝጋቢ መሆናቸውን የሚገልፅ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ።
  2. የመወዳደሪያ ደረጃቸውም GC/RC ደረጃ 7 እና ከዛ በላይ የሆኑ ተቋራጮች።
  3. በጨረታው ለመወዳደር የሚፈልጉ ተወዳዳሪዎች የሚገዙት ጨረታ ሰነዱን ጠቅሰው በማመልከቻ ሲጠይቁ ተወካዮች ከሆነ ከድርጅቱ ህጋዊ ውክልና ይዘው መምጣት አለባቸው።
  4. ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 21ኛው ተከታታይ ቀናት እስከ 8፡00 ሰዓት ድረስ የማይመለስ ብር 300/ሶስት መቶ ብር ብቻ በመክፈል የጨረታውን ሰነድ መሀልአምባ ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 03 ድረስ በመቅረብ መውሰድ ይችላሉ።
  5.  የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ ለ90 ቀናት ፀንቶ የሚቆይ ብር 100000 (መቶ ሺህ ብር) በገ/ጉ/ወ/ወ ፋይናንስ ፅ/ቤት ስም ማሰራት አለባቸው።
  6. ተጫራቾች የጨረታውን ቴክኒካል እና ፋይናንሻል ዶክመንት ሲያቀርቡ ሀ/ ለቴክኒካል ዶክመንት አንድ ኦርጅናል እና ሁለት ፎቶ ኮፒ በማድረግ ቴክኒካል በሚል በመለየት ለ/ ለፋይናንሻል ዶክመንት አንድ ኦርጅናል እና ሁለት ፎቶ ኮፒ በማድረግ ፋይናንሻል በሚል በመለየት በማሸግ ከላይ በተጠቀሰው የጨረታ ማስከበሪያ ሲፒኦ/ ከባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ከቴክኒካል ኦርጅናል ዶክመንቱ ጋር በማድረግ በማሸግ ቴክኒካል ዶክመንት በሚል በመለየት ይህ ማስታወቂያ አየር ላይ ከዋለበት ቀን ጀምሮ ባሉት 21 (ሀያ አንድ) ተከታታይ ቀናት መሀል አምባ የገ/ጉ/ወ/ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 03 ድረስ በመምጣት ለጨረታ አገልግሎት በተዘጋጀው ሳጥን ማስገባት ይኖርባቸዋል።
  7. የጨረታው ሰነድ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ21ኛው ተከታታይ ቀን በ8፡00 ሰዓት ታሽጎ በዚያኑ ቀን በ8፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል
  8. መስሪያ ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
  9. በጨረታው ሰነድ ላይ ምንም አይነት ስርዝ ድልዝ መኖር የለበትም።

ማሳሰቢያ:-

  1. በአፈፃፀም ምከንያት ማስጠንቀቂያ የተሰጣቸው ድርጅቶች መወዳደር አይችሉም።
  2. በወረዳው ውስጥ ሁለትና ከዚያ በላይ ፕሮጀክት ይዞ ስራውን ያልጨረሰ ተጫራች መወዳደር አይችልም።
  3. ተጫራቾች ሰነድ ለመግዛት ሲመጡ ከአሰሪው መስሪያ ቤት የሳይት ምልክታ ማየታቸውን የሚገልጽ ደብዳቤ ማቅረብ የሚችሉና።
  4. ጨረታው የሚከፈትበት ቀን በዓል ወይም ቅዳሜ ና እሁድ ከሆነ ወደሚቀጥለው የስራ ቀን ይዘዋወራል።
  5. አሸናፊው ድርጅት ቅድመ ክፍያ ሳይወስድ /ሳይጠይቅ ስራ መጀመር የሚችል።

ለበለጠ መረጃ የገ/ጉ/ወ ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት ቢሮ

ስልክ ቁጥር፡- 0113360162/146 ይደውሉ

የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት