
Sede Muja Woreda FEDB
በኩር
(Feb 03, 2025)
ለ2ኛ ጊዜ የወጣ ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
በደ/ጎንደር ዞን የሰዴ ሙጃ ወረዳ ገ/ኢ/ት/ጽ/ቤት ግን/አስ ቡድን ለ2017 በጀት አመት ለመንገድ ትራንስፖርት ጽ/ቤት አገልግሎት የሚውል የዶዘር ማሽን ኪራይ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡
ስለዚህ ከዚህ በታች የተዘረዘረውን መስፈርት ማሟላት የምትችሉ፡-
- በየዘርፉ ህጋዊ በዘመኑ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡
- የዘመኑን ግብር የከፈሉና /ቲን/ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- ተጫራቾች የሞሉት ዋጋ ከ200‚000.00 (ሁለት መቶ ሺህ ብር) በላይ ከሆነ ተጨማሪ እሴት ታክስ ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፍ ከላይ ከ1-3 የተጠቀሱትን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከጨረታ ሰነዱ ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች ሙሉ አድራሻቸውን በድርጅቱ ስም የተዘጋጀ ማህተም መምታት አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነዱን የማይመለስ 50 /አምሳ / ብር በመክፈል ከመ/ቤታችን ገንዘብ ያዥ ቢሮ ቁጥር 04 ዘወትር በስራ ቀን መግዛት ይችላሉ፡፡
- የሚገዙ እቃዎችን አይነትና ዝርዝር መግለጫ ስፔስፊኬሽን ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይቻላል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ለሚወዳደሩበት የእቃውን ጠቅላላ ዋጋ አንድ በመቶ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ /ሲፒኦ/ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም በጥሬ ገንዘብ በመሂ 1 ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች ጨረታውን ካሸነፉ በኃላ አስር በመቶ የውል ማስከበሪያ በጥሬ ገንዘብ በባንክ በተረጋገጠ /ሲፒኦ/ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ጨረታው ለ15 ተከታታይ ቀን በአየር ላይ ይውላል፡፡
- ጨረታው በ16ኛው ቀን በ3፡00 ይታሸጋል በዚሁ ቀን ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ግ/ን/አስ ቢሮ ቁጥር 2 በዚሁ ቀን 3፡30 ይከፈታል፡፡ ተጫራቾች (ህጋዊ ወኪሎቻቸው) ጨረታው በሚከፈትበት ቀን ቢገኙም ባይገኙም ጨረታውን ለመክፈት አያስተጓጉልም፡፡
- ከጨረታ ሰነዱ ላይ ሥርዝ ድልዝ መሆን የለበትም፡፡
- ጨረታው የሚከፈትበት የበዓል ቀን ከሆነ በቀጣይ የሥራ ቀን ይከፈታል፡፡
- በማስታወቂያ ያልተገለጹ ካሉ በግዥ መመሪያው መሰረት ተፈጻሚ ይሆናሉ፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው፡፡
- የመልካም ሥራ አፈጻጸም መገለጫ እና ሊብሬ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- ጨረታውን ለማዛባት የሚሞክሩ ተጫራቾች ከጨረታ ውጭ እንደሚሆኑ ለወደፊቱም በመንግስት ጨረታ እዳይሳተፉ የሚደረጉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡
- የጨረታ ጊዜ ከተጠናቀቀ በኋላ ተጫራቾች ባቀረቡት የማወዳደርያ ሃሳብ ላይ ለወጥ (ማሻሻያ) ማድረግና ከጨረታው እራሳቸውን ማግለል አይችሉም፡፡
- ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ግ/ን/አስ ቢሮ ቁጥር 2 ድረስ በአካል በመቅረብ ወይም በስሥልክ ቁጥር 09 18 28 07 69 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል፡፡
የሰዴ ሙጃ ወረዳ ገ/ኢ/ት/ጽ/ቤት