
Kolfe Keranyo Sub City Beruh Tesfa primary school
አዲስ ዘመን
(Feb 05, 2025)
የጨረታ ማስታወቂያ
የግዥ መለያ ቁጥር 002/2017
የኮልፌ ቀራኒዮ ክ/ከተማ ለብሩህ ተስፋ የመ/ደ/ት/ቤት ለ2017 የስራ ዘመን ለጽዳት እና ንጽህና መስጫ መሳሪያዎች፣ የደንብ ልብስ፣ አላቂ የቢሮ እቃዎች፣ ህትመት፣ ሌሎች አላቂ እቃዎችን ፕላንት ማሽነሪ ቁሳቁስ እና ተገጣጣሚዎችን በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
ተ.ቁ | የእቃው አይነት | የጨረታ ማስከበርያ ዋስትና(CPO) |
ሎት 1 | የደንብ ልብሶች | 2000.00 (ሁለት ሺህ ብር) |
ሎት 2 | አላቂ የቢሮ እቃዎች | 2,500.00 (ሁለት ሺህ አምስት መቶ ብር) |
ሎት 3 | ህትመት | 500.00 (አምስት መቶ ብር) |
ሎት 4 | ሌሎች አላቂ እቃዎች | 600.00 (ስድስት መቶ ብር) |
ሎት 5 | ፕላን ማሽነሪ የሚገዙ እቃዎች | 2000.00 (ሁለት ሺህ ብር) |
ሎት 6 | ለቁሳቁስ እና ለተገጣጣሚዎች | 2500.00 (ሁለት ሺህ አምስት መቶ ብር) |
በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች ከዚህ በታች የተገለጹትን መስፈርቶች አሟልተው ማቅረብ አለባቸው፤
1. በዘርፉ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸውና የዘመኑን ግብር ለመክፈላቸው ማስረጃ የሚያቀርቡ መሆን አለባቸው፤
2. በገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር (በመንግስት ግዥ ኤጀንሲ ድረ–ገጽ ላይ የተመዘገቡበትን የአቅራቢነት ኮፒ) ማቅረብ አለባቸው፤
3. ተጫራቾች በጨረታው መሳተፍ የሚችሉ መሆኑን ከኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ወይም ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አካላት የድጋፍ ደብዳቤ የሚያቀርቡ፣ የተጨማሪ አሴት ታክስ የተመዘገቡበትን የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ መሆን አለባቸው፡፡
4. ተጫራቾች ለሚያቀርቧቸው ዕቃዎች ለእያንዳንዱ የእቃ ጨረታ ከመከፈቱ በፊት ናሙና የማቅረብ ግዴታ አለባቸው፤
5. ተጫራቾች የጨረታ ሰነድ ኦርጅናል እና ኮፒ ፖስታዎችን ለየብቻ በማሸግ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
6. ተጫራቾች የማጭበርበር ድርጊት ላለመፈጸም ቃል የሚገቡበትን ፎርማት በመሙላት የተጫራቾችን ድርጅት ፊርማ እና ማህተም በማድረግ ማቅረብ አለባቸው፤
- ተጫራቾች ከላይ በሰንጠረዡ የተገለጹትን የገንዘብ መጠን የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ጋራንቲ ወይም በባንክ በተረጋገጠ CPO ማቅረብ አለባቸው፡፡
- ጨረታው ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት የመጀመሪያው ቀን አንስቶ ለ10 ተከታታይ የስራ ቀናት ድረስ ክፍት ሆኖ ይቆይና በ11ኛው ቀን በኢትዮጵያ ሰአት አቆጣጠር ጠዋት 4፡00 ሰዓት ታሽጎ በ4፡30 ሰዓት ምክትል ርዕሰ መምህር ቢሮ ይከፈታል፤
- በጨረታው ለመሳተፍ ፍላጎት ያላቸው ተጫራቾች የማይመለስ ብር 100 (አንድ መቶ ብር) በመክፈል የጨረታ ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በት/ቤቱ ግዥ ክፍል ቢሮ ቁጥር 1 ሰነዱን መውሰድ ይችላሉ፤
- ተጫራቾች የሚወዳደሩበትን የጨረታ ሰነድ በሰንጠረዡ በተጠቀሰው የጨረታ መዝጊያ ቀንና ሰአት በፊት በግዥ ክፍል ለዚሁ በተዘጋጀ የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይችላሉ፡፡
- ጨረታው ከላይ በተገለጸው የመክፈቻ ቀንና ሰአት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በት/ቤቱ ምክትል ርዕሰ መምህር ይከፈታል፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- በጨረታው አሸናፊ የሆነው አካል ያሸነፈባቸውን እቃዎች መስሪያ ቤቱ ድረስ በራሱ ትራንስፖርት ማቅረብ ይኖርበታል።
አድራሻ፡– ኮ/ቀ./ክ/ከ ብሩህ ተስፋ የመ/ጀ/ደ/ት/ቤት ከአለርት ሆስፒታል ጀርባ፡፡
ለበለጠ መረጃ 0113-21-13-94/0113-69-95-35
በኮልፌ ቀራኒዮ ክ/ከተማ ወረዳ 01 የብሩህ ተስፋ የመ/ደ/ት/ቤት