
Gurage Zone Meskan Woreda F/E/D/Bureau
አዲስ ዘመን
(Feb 05, 2025)
ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ
በምስራቅ ጉራጌ ዞን የመስቃን ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት በ2017 በጀት ዓመት በካፒታል በጀት ለተለያዩ ሴክተር መ/ቤቶች ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ዕቃዎች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
ሎት፡– 1 የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች፤
- ተጫራቾች ሕጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸውና የዘመኑን ግብር የከፈሉና የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር ያላቸው መሆን ይጠበቅባቸዋል፡፡
- የእቃው አቅራቢነት ምዝገባ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ መሆን አለባቸው፤
- የተጨማሪ እሴት ታክስ የምዝገባ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- ተጫራቾች ስለ ጨረታው ዝርዝር የያዘውን ሰነድ ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የእቃዎቹን ስፔስፊኬሽን በተገለጸው መሰረት ተሞልቶ እንዲገለጽና ለሎት 1 የማይመለስ 100 /አንድ መቶ ብር ብቻ/ በመክፈል ዘወትር በስራ ሰዓት የመ/ወ/ፋ/ጽ/ቤት በመቅረብ የተዘጋጀውን ሰነድ መግዛት የሚችሉ መሆን አለባቸው፤
- ተጫራቾች ከሚያቀርቡት ዋጋ ጋር ተመጣጣኝ የሆነ የጨረታ ማስከበሪያ ብር 10000 /አስር ሺህ/ በባንክ በተመሰከረለት /CPO/ወይም በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የሚያቀርቡት ዋጋ በተዘጋጁት ዝርዝር ስፔስፊኬሽን ላይ ሞልተው በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 ተከታታይ ቀናት መ/ቤቱ ባዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው፡፡ ጨረታው የጨረታው ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ16ኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዕለቱ ከጠዋቱ 4፡30 ሰዓት ተጫራቾች /ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ጨረታው ይከፈታል፡፡ ቀኑ ቅዳሜና እሁድ ወይም የበዓል ቀን ከሆነ በቀጣዩ የስራ ቀን ካላይ በተገለጸው ሰዓት ይከፈታል፤ የተጫራቾች አለመኖር ፖስታው ተሟልቶ እስከተገኘ ድረስ ጨረታውን ከመክፈት አያስተጓጉልም፡፡
- አሸናፊው ድርጅት እቃውን ወረዳው ፋይናንስ ድረስ በማምጣት ማስረከብ ይጠበቅበታል፡፡
- መስሪያ ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለበለጠ በረጃ በስልክ ቁጥር 046 115 1102 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡
በማ/ኢ/ክ/መ በምስራቅ ጉራጌ ዞን የመስቃን ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት