
Defense Construction Enterprise (DCE)
አዲስ ዘመን
(Jan 26, 2025)
የጨረታ ማስታወቂያ
የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ ለቆሬ ዋር ኮሌጅ አገልግሎት የሚውሉ Supply and fix perforated metal Armstrong orcal metal ceiling 600×600×33mm and perforated metal Armstrong ceiling aluminum 600×600×1.2mm ግዥ አስመልከቶ ተጫራቾችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
ተ.ቁ | የዕቃው ዓይነት | የጨረታ ቁጥር | የጨረታ መዝጊያ ቀን እና ሰዓት | የጨረታ መክፈቻ ቀን እና ሰዓት | የጨረታ ማስከበሪያ |
1 | Supply and fix perforated metal Armstrong orcal metal ceiling 600x600x33mm and perforated metal Armstrong ceiling aluminum 600x600x1.2mm | DCE/ SF/35/2025
| የካቲት 07/2017 ዓ.ም ከቀኑ 8፡15 ሰዓት | የካቲት 07/2017 ዓ.ም ከቀኑ 8፡30 ሰዓት | 100,000,00
|
ስለሆነም።
- ተጫራቾች በዘርፍ የተሰማሩ መሆኑን የሚገልጽ የታደሰ የንግድ ፈቃድ፣ የንግድ ምዝገባ የምስክር ወረቀት፣ የዘመኑን ግብር የከፈሉበት ማስረጃ፣ ለተጨማሪ እሴት ታክስ የተመዘገቡበትን የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር፣ በጨረታ ለመሳተፍ የሚሰጥ የታደሰ የምስክር ወረቀት (ታከስ ከሊራንስ) እና የአገር ውስጥ ተጫራቾች በአቅራቢዎች ዝርዝር ውስጥ የተመዘገቡ መሆኑን የሚያረጋግጥ ኮፒ ወዘተ…ማቅረብ የሚችሉ መሆን አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ከላይ በሰንጠረዥ በተገለፀው መሰረት በባንክ የተረጋገጠ (CPO) ወይም ከታወቀ ባንከ በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና (Unconditional Bank Guarantee) ለ120 (አንድ መቶ ሃያ) Calendar days ፀንቶ የሚቆይ ከመጫረቻ ሰነዳቸው ጋር ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 200.00 /ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል ዘወትር በሥራ ሰዓት ቃሊቲ ቶታል ከኢዲሱ ስታዲየም ጀርባ ወይም ኮማንደር አትሌት ደራርቱ ቱሉ ት/ቤት አጠገብ በሚገኘው የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ ዋና መ/ቤት የግዥና አቅርቦት አስተዳደር መምሪያ ቢሮ መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የሚያቀርቡት ዋጋ በጨረታ ሰነድ በተያያዘው ዝርዝር እና ብዛት መሠረት መሆን ይኖርበታል፡፡
- ተጫራቾች የሚወዳደሩበትን የጨረታ ቴክኒካል ሰነድ እና ዋጋ በታሸገ ኤንቨሎፕ ከላይ በሰንጠረዡ በተገለፀው ቀንና ሰዓት በኢንተርፕራይዙ የግዥና አቅርቦት አስተዳደር መምሪያ ቢሮ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ጨረታው ከላይ በሰንጠረዡ በተገለፀው መሠረት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በድርጅቱ መሰብሰቢያ አዳራሽ ይከፈታል፡፡
- ኢንተርፕራይዙ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
አድራሻ፡– የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ
ቃሊቲ ቶታል ከአዲሱ ስታዲየም ጀርባ ወይም
ኮማንደር አትሌት ደራርቱ ቱሉ ት/ቤት አጠገብ
የቀጥታ ስልክ ቁፕ 0114-40-3434
ማዞሪያ 011442-22-70/71/72
Email አድራሻ Info@dce-et.com
የድረ ገፅ አድራሻ www.dce-et.com
የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ