Wro. Beleteshachew Health Center
አዲስ ዘመን
(Sep 14, 2024)
ግልፅ ጨረታ ማስታወቂያ
የገዥው መለያ ቁጥር 01/2017
በልደታ ክፍለ ከተማ የወ/ሮ በለጥሻቸው ጤና ጣቢያ በ2017ዓ.ም በጀት ዓመት የሚፈልጋቸውን
- ሎት 1- የተለያዩ የደንብ ልብስ የጨረታ ማስከበሪያ በብር 4000.00
- ሎት 2፡– የፅህፈት መሳሪያ የጨረታ ማስከበሪያ ብር 4000.00
- ሎት 3፡– የህትመት ጨረታ ማስከበሪያ በብር 3000.00
- ሎት 4፡– የፅዳት ዕቃዎች የጨረታ ማስከበሪያ ብር 4000.00
- ሎት 5፡– የጥገና እቃዎች የጨረታ ማስከበሪያ ብር 4000.00
- ሎት 6፡– ቋሚ የኤሌክትሪክ ዕቃዎች የጨረታ ማስከበሪርያ ብር 5000.00
- ሎት 7- ቋሚ የፈርኒቸር ዕቃዎች የጨረታ ማስከበሪያ ብር 5000.00
- ሎት 8፡– የተሸከርካሪ የኪራይ አገልግሎት የጨረታ ማስከበሪያ ብር 5000.00
- ሎት 9፡– የመድሀኒትና ላብራቶሪ ሪኤጀንቶች የጨረታ ማስከበሪያ ብር 5000.00
- ሎት 10- የተለያዩ የደንብ ልብስ ስፌት የጨረታ ማስከበሪያ በብር 4000.00
ብቃት ያላቸው በመስኩ የተሰማሩ ተጫራቾችን አወዳድሮ ግዥ/አገልግሎት መፈፀም ይፈልጋል። በዚህም መሰረት፣
- በጨረታው ለመወዳደር ፍላጎት ያላቸው ተጫራቾች የታደሰ ንግድ ፍቃድ ፣ የዘመኑን ግብር የከፈሉ፣ በመንግስት ግ/ን/አስ/ኤጀንሲ ድህረ ገፅ ላይ በአቅራቢዎች ምዝገባ ዝርዝር የተመዘገበ የቲንና የቫት ተመዝጋቢ የሆኑና የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ ከጨረታው ሰነዳቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ዕለት አንስቶ ለተከታታይ 10 የስራ ቀናት የማይመለስ ብር 200 (ሁለት መቶ ብር) በመክፈል በልደታ ክፍለ ከተማ የወ/ሮ በለጥሻቸው የህዝብ ጤና ጣቢያ አዲሱ ህንፃ አንደኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 38 ( ፋይናንስ) ቢሮ በመምጣት የጨረታ ሰነዱን መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነዳቸውን በታሸገ ኢንቨሎፕ ማስታወቂያ ከወጣበት እለት ጀምሮ ለተከታታይ 10 የስራ ቀናት ለጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በአስራ አንደኛው ቀን በ4፡00 ሰዓት ታሽጎ በዕለቱ ከቀኑ 4፡30 ሰዓት በወ/ሮ በለጥሻቸው ጤና ጣቢያ አዲሱ ህንፃ ሁለተኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 43 ይከፈታል የመክፈቻ ቀኑ ቅዳሜና እሁድ ወይም የበዐል ቀን ከሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ታሽጎ ይከፈታል፡፡ ተጫራቾች የሚወዳደሩባቸውን እቃዎች ለእያንዳንዱ ከቫት ውጪና ከቫት ጋር ያለውን ዋጋ ማስቀመጥ ይኖርባቸዋል ፡፡
- የዘገየ ጨረታና በመከፈቻው ላይ ያልተነበበ ጨረታ ተቀባይነት የለውም ፡፡
- ተጫራቾች ጨረታው ከመዘጋቱ በፊት ባሉት ቀናቶች የተወዳደሩበትን ዕቃ ናሙና ማስገባት አለባቸው ናሙና ያልቀረበበት ጨረታ ዋጋ አይኖረውም፡፡
- አሸናፊ ተጫራጮች ያሸነፉባቸውን እቃዎች በራሳቸው ትራንስፖርት ግዥ ፈፃሚው መስሪያ ቤት ድረስ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
- መስሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለተጨማሪ ማብራሪያ ጥያቄ በልደታ ክፍለ ከተማ ጤና ጣቢያ ወ/ሮ በለጥሻቸው የህዝብ ጤና ጣቢያ የመ/ቤት
ስልክ 011-8-54-92-37
በልደታ ክፍለ ከተማ የወ/ሮ በለጥሻቸው ጤና ጣቢያ