• Somali

Customs Commission Jigijiga Branch

አዲስ ዘመን
(Sep 01, 2023)

የግልጽ እና የሐራጅ ጨረታ ማስታወቂያ

የጉምሩክ ኮሚሽን ጅግጅጋ ቅ/ጽ/ቤት በኮንትሮባንድ የተያዙ ተሽከርካሪዎችን በግልጽ እና በሐራጅ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ ለጨረታ የቀረቡትን ተሽከርካሪዎች ከ26/12/2015 ዓ.ም ጀምሮ በማየት እና ከዚህ ቀጥሎ የተገለጹትን መስፈርቶች በማሟላት መወዳደር የምትችሉ መሆኑን ቅ/ጽ/ቤቱ ይገልጻል፡፡

ስለሆነም በጨረታው ላይ ለመካፈል የምትፈልጉ ተጫራቾች፡-

  1. የነዋሪነት መታወቂያ ያለው ማንኛውም ኢትዮጵያዊ፤
  2. ለሐራጅ ጨረታው ለእያንዳንዱ መኪና 100,00 (አንድ መቶ ሺህ) የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ሲፒኦ (CPO) ማስያዝ የሚችል፤
  3. በግልጽ ጨረታ ለመሳተፍ ተሽከርካሪውን ለመግዛት የሚያቀርበውን የመጫረቻ ዋጋ አምስት በመቶ (5%) ሲፒኦ (CPO) ማቅረብ የሚችል፤
  4. ተጫራቹ ለሐራጅ ጨረታ ለእያንዳንዱ መኪና የሚገዛበትን መነሻ ዋጋ እራሱ ያቀርባል።
  5. ለግልጽ ጨረታ ቅ/ጽ/ቤቱ ካስቀመጠው መነሻ ዋጋ ተነስቶ ዋጋ በመሙላት በተቀመጠው ሣጥን ውስጥ ማስገባት የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
  6. ተጫራቹ በጨረታው አሸንፎ የገዛውን መኪና ወዲያውኑ ከፍሎ በ5 ቀን ውስጥ የሚረከብ መሆን አለበት።
  7. መኪናውን አሸንፎ የገዛ ተጫራች የሚፈለግበትን ዋጋ ወዲያውኑ ከፍሎ በ5 ቀን ውስጥ ካልተረከበ ያስያዘው ሲፒኦ (CPO) ለመንግሥት ገቢ ይሆናል።
  8. በጨረታው ያላሸነፉ ተጫራቾች ያስያዙት ሲፒኦ (CPO) ወዲያውኑ ይመለስላቸዋል።
  9. ማንኛውም ተጫራች የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጅግጅጋ ቅርንጫፍ ሲፒኦ (CPO) አሠርቶ ማምጣት አለበት።
  10. አሳማኝ የሆነ ምከንያት ከተገኘ እና በመ/ቤቱ ተቀባይነት ካላገኘ ጨረታውን መሰረዝ ይችላል።
  11. ማንኛውም ተጫራች መኪናውን ካሸነፈ በኋላ ከጅግጅጋ ውጪ ለማጓጓዝ ቢፈልግ እንደየቦታው እርቀት በቀነ ገደብ መሸኛ ሊሰጣቸው ይችላል።
  12. ተጫራቹ መኪናውን አሸንፎ ከተረከበ በኋላ መሸኛ ሳይዝ የትም ቦታ ቢያዝ መ/ቤቱ ኃላፊነቱን አይወስድም።
  13. ተጫራቾቹ የሞሉትን የጨረታ ሰነድ በ2/13/2015 ከጠዋቱ 2፡00 ሰዓት እስከ 3፡45 ሰዓት በጅግጅጋ ጉ/ኮ/ቅ/ጽ/ቤት ማስገቢያ ሣጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፤ ጨረታው 3፡45 ሰዓት ተዘግቶ በ2/13/2015 ዓ.ም ከረፋዱ 4፡00 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ሚከፈት ይሆናል።
  14. የሐራጅ ጨረታው የሚካሄደው በ2/13/2015 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡30 ሰዓት መሰብሰቢያ አዳራሽ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይሆናል።

ማሳሰቢያ፡- አሸናፊው የተጨማሪ እሴት ታክስ /ቫት/ 15% /አስራ አምስት ፐርሰንት/ የሚከፍል መሆኑ ይታወቅ፤ መኪናውን ሳያዩ የሚጫረቱ ተጫራቾች ቅ/ጽ/ቤቱ ኃላፊነቱን አይወስድም።

የጉምሩክ ኮሚሽን ጅግጅጋ ቅ/ጽ/ቤት